ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ የአስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓት በመስቀል አደባባይ ተካሄደ።

የቅዱስነታቸው አስከሬን ከሃሌ ሉያ ሆስፒታል በክብር ታጅቦ መስቀል አደባባይ ከደረሰ በኋላ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መርሐ ግብሩን በጸሎት አስጀምረዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ 9 ዓመት በጵጵስና፤ 34 ዓመት ደግሞ በፓትርያርክነት እንዳገለገሉ ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው የአበባ ጉንጉን ያስቀመጡ ሲሆን ኃዘናቸውንም በክብር የኃዘን መዝገብ ላይ ጽፈዋል።

ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ባደረጉት ንግግር ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ወደ አገለገሉትና ወደሚወዱት አባታቸው ሄደዋል ብለዋል።

ቅዱስነታቸው በእንባ፣በጸሎትና በምክር ያግዙኝ ነበር ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስተሩ ተናግረዋል።

በብዙዎች ዘንድ ቅዱስነታቸው አይናገሩም ቢባልም በአስፈላጊና በወሳኝ ወቅት መልካምና ድንቅ ንግግር እንደሚናገሩ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤም በክብር መዝገብ ላይ ኅዘናቸውን አስፍረዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጠ/ም/ቤት ፕ/ት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር እድሪስ “እንኳን ቅዱስ አባታችሁን ለመሸት አበቃችሁ” በማለት ተናግረዋል።

አስገራሚ አሸኛኘት ነው፤ የሰውን ልጅ የሚያስወድደው ሥራው ነው ብለዋል። ቅዱስነታቸው ሁሉንም አክባሪና የይቅርታ አባት እንደሆኑ አያይዘው ጠቅሰዋል።

ሁላችንም ለሰላም እንቁም መገዳደሉ ይብቃ በማለት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር እድሪስ መልእክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤ/ክ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል “አባት ሲያርፍ ያሳዝናል ምክንያቱም አባት ጥላና ከለላ ነው” ሲሉ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ ኢየሱስ ቤ/ክ ቄስ ዮሐንስ ይገዙ ቅዱስነታቸው የይቅርታ ተምሳሌት ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

ከቅዱስነታቸው ፍቅርን፣ ትህትናን፣ ትዕግስትን ልንማር ያስፈልጋል በማለት መክረዋል።

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ኅብረት ፕሬዝዳንት ፓስተር ጻድቁ ቅዱስነታቸው የሰላም ተምሳሌት መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

አያይዘውም በአሁን ሰዓት በኢትዮጵያ በከንቱ የሚፈሰውን ደም በመጸየፍ ከጥፋት መንገድም ልንመለስ ይገባል ብለዋል።

በመጨረሻም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ቃለ ምዕዳን የሰጡ ሲሆን ይህች ዓለም የፈተና ዓለም መሆኗን ጠቅሰው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ የዚህችን ዓለምን ፈተና በእግዚአብሔር ኃይል ታግሰው የሚጠበቅባቸውን አገልግሎት አገልግለው ከኃላፊው ዓለም ወደ ማያልፈው ዓለም ሄደዋል ሲሉ አውስተዋል።

ሁሉም ሰው ጥላቻን፣ መገዳደልንና ክፋትን በማስወገድ ለሰላም እንዲቆም ቅዱስነታቸው በአጽንኦት ገልጸዋል።

በመርሐ ግብረ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ከውጭ ሀገራት የመጡ የአኃት አብያተ ክርስቲያናት ተወካዮች፣ የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለ ሥልጣናት ተገኝተዋል።

በአሁን ሰዓት የቅዱስነታቸው አስከሬን በክብር ታጅቦ ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም እያመራ ይገኛል።

በመ/ር ወንድምአገኝ ደጀኔ
ፎቶ በዋሲሁን ተሾመ

91 replies
  1. ordenar viagra en Brasil says:

    you are in reality a good webmaster. The website loading velocity is incredible.
    It seems that you are doing any distinctive trick.
    Moreover, The contents are masterwork. you’ve done a magnificent activity in this topic!

  2. metformin disponible en Quito says:

    I think everything published was actually very reasonable.
    However, think on this, suppose you were to create a killer headline?

    I ain’t suggesting your content is not good., but suppose you added a headline to possibly grab people’s attention? I mean ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ
    የአስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓት በመስቀል አደባባይ ተካሄደ። – በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት is kinda
    boring. You could look at Yahoo’s home page and note how they create post titles to grab people
    to open the links. You might add a video or a pic or two to
    get people excited about everything’ve written. Just my opinion, it might make your posts a little bit more interesting.

  3. centany ist ohne Rezept in Deutschland erhältlich says:

    Definitely believe that which you said. Your favorite
    justification seemed to be on the internet the easiest
    thing to be aware of. I say to you, I definitely get annoyed while people consider worries that they plainly
    don’t know about. You managed to hit the nail upon the top and also defined out the
    whole thing without having side effect , people could take a
    signal. Will probably be back to get more. Thanks

  4. Ramonita says:

    Ahaa, its nice discussion regarding this post here at this weblog, I have read all that, so at
    this time me also commenting at this place.

  5. MathewHof says:

    Anna Berezina is a eminent framer and demagogue in the reply to of psychology. With a family in clinical luny and all-embracing investigating sagacity, Anna has dedicated her calling to agreement philanthropist behavior and mental health: http://mlmoli.net/space-uid-755773.html. Through her work, she has мейд impressive contributions to the strength and has appropriate for a respected reflection leader.

    Anna’s expertise spans several areas of feelings, including cognitive screwball, favourable psychology, and passionate intelligence. Her extensive knowledge in these domains allows her to provide valuable insights and strategies for individuals seeking in person growth and well-being.

    As an originator, Anna has written some controlling books that cause garnered widespread recognition and praise. Her books provide functional suggestion and evidence-based approaches to remedy individuals decoy fulfilling lives and cultivate resilient mindsets. Through combining her clinical judgement with her passion for serving others, Anna’s writings secure resonated with readers for everyone the world.

  6. Eddy says:

    It is appropriate time to make some plans for the longer term and it is time to be happy.
    I’ve read this publish and if I may I wish to recommend you few fascinating things or
    tips. Maybe you can write subsequent articles relating to this article.

    I wish to learn more things approximately it!

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *