ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ሠራተኞች ጋር ትውውቅ በማድረግ የሥራ መመሪያ ሰጡ!

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ከሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መጋቤ አእላፍ በላይ ፀጋዬ ጋር በመሆን ከሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ሠራተኞች ጋር ትውውቅ በማድረግ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ እኛ መልእክተኞች ነን፣ ከላይ ተልከን ቤተ ክርስቲያንን እንድናገለግል መጥተናል ስለዚህ በሀገረ ስብከቱ የነበረው መልካም ገጽታ በማስቀጠል ስህተቱን ደግሞ በማረም እንሠራለን ብለዋል።

ብፁዕነታቸው ሀገረ ስብከቱ ትልቅና በሀገሪቱ መዲና የሚገኝ ቢሆንም በብዙዎች ዘንድ ግን በመልካም ስም እንደማይነሳ ገልጸዋል።

አያይዘውም ሀገረ ስብከቱ ለምን ታመመ ሲሉ በመጠየቅ መድኃኒት እንደሚያስፈልገው ጠቅሰው አሁን መልካም ስም እንዲኖረው በጋራ ሆነን ፈውስ እናበጅለት ዘንድ ይገባል ሲሉ ተደምጠዋል።

ሀገረ ስብከቱ ተሻጋሪ ራዕይ ሊኖረው ይገባል፣ራሱን ችሎ የስብከተ ወንጌልመርሐግብር እንደ አድባራቱና ገዳማቱ ማዘጋጀች አለበት በማለት አብራርተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ሀገረ ስብከቱ ከፐርሰንት ውጪ የራሱ የሆነ የገቢ ምንጭ እና መንበረ ጵጵስና እንዲኖረው እንሠራለን ሲሉም ገልጸዋል።

የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መጋቤ አእላፍ በላይ ፀጋዬ በሀገረ ስብከቱም ሆነ በአጠቃላይ በቤተ ክርስቲያን ብልሹ አሠራር የሚፈጠረው ኃላፊነታችን ሳንወጣ ስንቀር መሆኑን በመግለጽ የተሰጠንን ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት የብፁዕ አባታችን መመሪያ ተቀብለን የሀገረ ስብከቱ መልካም ገጽታ ለመገንባት በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ተደግፈን የአቅማችን እንሠራለን ሲሉ ተናግረዋል።

ከሀገረ ስብከቱ ሠራተኞችም ሐሳብ የተሰጠ ሲሆን ብፁዕነታቸው ካዳመጡ በኋላ የተሰጡትን አስተያየቶች አድንቀው ሥራቸውን ለመሥራት እንደግብአት እንደሚጠቅማቸው ገልጸዋል።

ሀገረ ስብከቱ ለአንዱ የቤት ልጅ ለአንዱ የእንጀራ ልጅ እንደማይሆን በመግለጽ ሥራቸውን ጥናት በማካሄድ እንደሚጀምሩና በየጊዜው ከሠራተኞች ጋር ግምገማና ውይይት እንደሚኖር ተናግረዋል።

በመጨረሻም በፁዕነታቸው አሁን ላገለግል መጥቻለሁ የሀገረ ስብከቱ መልካም ስም ይመለስ ዘንድ አብረን እናገለግላለን፣ እኔ ተመሳስዬና አስመስሎ መሥራት አልፈልግም ሲሉ ገልጸዋል።

የአቅሜን ያህል ቤተ ክርስቲያንን የሚጠቅም በእውነትና በትክክል እሠራለሁ እናንተም ልጆቼ ልትመስሉኝና ልትከተሉኝ ይገባል ሲሉ አባታዊ መመሪያና መልእክት አስተላልፈዋል።

14 replies
  1. anksilon à commander sans ordonnance says:

    You really make it seem so easy with your presentation but I
    find this topic to be actually something that I think I would never
    understand. It seems too complicated and very broad for me.

    I’m looking forward for your next post, I will try to get the hang of
    it!

  2. depo-provera prescrit sur ordonnance says:

    Definitely consider that that you said. Your favourite
    reason seemed to be at the net the simplest factor to
    remember of. I say to you, I certainly get annoyed while other folks consider
    worries that they plainly do not realize about. You managed to hit the nail upon the highest as smartly
    as outlined out the entire thing without having side effect
    , folks could take a signal. Will likely be again to get more.
    Thanks

  3. acyclovir sin receta says:

    I do consider all of the ideas you’ve offered to your post.
    They’re very convincing and will definitely work.
    Nonetheless, the posts are very quick for beginners.
    May just you please prolong them a bit from subsequent time?
    Thanks for the post.

  4. baclofen rezeptfrei erhältlich in Paris says:

    Hmm it seems like your blog ate my first comment
    (it was super long) so I guess I’ll just sum it up what I submitted and say, I’m
    thoroughly enjoying your blog. I as well am
    an aspiring blog writer but I’m still new to the whole thing.
    Do you have any recommendations for rookie blog writers?

    I’d certainly appreciate it.

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *